ዋሺንግተን ዲሲ —
የዓለም ምጣኔ ሀብት ካለፈው ዓመት በተሻለ ዕድገት ይቀጥላል ሲል፤ የዓለም የገንዘብ ድርጅት አይ ኤም ኤፍ /IMF/ የምጣኔ ዕድገት ትንበያ አስታወቀ። በዚህም መሰረት ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት በተመሳሳይ ወቅት ወጥቶ ከነበረው ዝቅተኛ የ4.5 ከመቶ ዕድገት በቀጣዩ ዓመት በ7.5% እንደምታድግ ሲተነብይ ኤርትራ በ3.3 ከመቶ አጠቃላይ አፍሪካ ደግሞ በአማካይ 3.5 ከመቶ የሆነ ዕድገት እንደሚያስመዘግቡ ተቀምጧል።
በዋሽንግተን ዲሲ በዛሬው ዕለት የተጀመረውን የዓለም ባንክና የዓለም የገንዘብ ድርጅት ጉባዔ ተከታትሎ ሔኖክ ሰማእግዜር ቀጣዩን ዘግቧል።
ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ