በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በምዕራብ ወለጋ የግንኙነት መረብ መቋረጥ - የሂዩማን ራይትስ ወች መግለጫና የመንግስት ምላሽ


በአዲስ አበባ አንዲት በጎፈቃደኛ የኮረናቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የእጅ ማፅጃ ወደ አውቶብስ ውስጥ ለሚሳፈሩ ሰዎች እየሰጠች © AP Photo/Mulugeta Ayene
በአዲስ አበባ አንዲት በጎፈቃደኛ የኮረናቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የእጅ ማፅጃ ወደ አውቶብስ ውስጥ ለሚሳፈሩ ሰዎች እየሰጠች © AP Photo/Mulugeta Ayene

በምዕራብ ኦሮሚያ የሚገኙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ስልክና ኢንተርኔትስለተቋረጠባቸው ኮረና ቫይረስን ለመከላከል የሚያስችላቸውን መረጃ ከሌሎች ኢትዮጵያውያንእኩል እንዳያገኙ ተደርገዋል ሲል ሂዩማን ራይትስ ወች የኢትዮጵያ መንግስትን ወቀሰ።

የብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ጽ/ቤት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ታዬ ደንዳ በበኩላቸው “የኦነግ ሸኔ በሚል የሚጠራው የታጠቀ ቡድን ስልክና ኢንተርኔትን በመጠቀም ባደራጃቸው የትስስር ሰንሰለት በሕዝብ ላይ እጅግ ዘግናኝ ድርጊቶችን ሲፈፅም መቆየቱን ገልፀው፤ ይህ ሰንሰለት ከላይ እስከ ታች የተቋረጠባቸውና ቡድኑ የተዳከመባቸው ኃይሎች በኮረና ቫይረስ አሳበው ኢንተርኔቱን በጩኸት ለማስመለስ የያዙት ጥረት ነው “ ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

ስለ ኮረና ቫይረስ ወረርሽኝ የሚያስፈልገውን መረጃ መንግስት በራዲዮ፣በቴሌቭዥን እና በጤና ኤክስቴንሽን ባለሞያዎች አማካኝነት ለኅብረተሰቡ እንዲደርስ እያደረገ ነው ብለዋል። የሂዩማንራይትስ ወች የአፍሪካ ቀንድ ተመራማሪ ላቲሺያ ባይደር ዜጎችን ከጥቃት የመከላከልም ሆነ የስልክና የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ የመንግስት ግዴታ ነው ብለዋል።

(ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ)

በምዕራብ ወለጋ የግንኙነት መረብ መቋረጥ - የሂዩማን ራይትስ ወች መግለጫና የመንግስት ምላሽ
please wait

No media source currently available

0:00 0:08:51 0:00


ረቡዕ​ መጋቢት 25, 2020 ተላልፎ የነበረውን መሰናዶም ማስፈንጠሪያውን በመጫን

ማዳመጥ ይቻላል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG