በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሃዋሳ ከተማ ዕጣ ፈንታ


የሃዋሳ ከተማ ዕጣ ፈንታ በአብሮነት ላይ የተመሠረተ ስለሆነ በወቅታዊ ፖሊቲካ ጉዳዮች ለነዋሪዎች ሥጋት ሊሆን እንደማይገባ የደቡብ ክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ ተናገሩ፡፡

ለአንዱ የተሻለ ዕድል ተሰጥቶ የተቀረውን ወገን መከልከል ታሪካዊ ስህተት መፈፀም ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ሃዋሳን ለሁሉም የምትመች ከተማ ለማድረግ ተደጋግፎ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

የከተማዋ አስተዳደር በወቅታዊ የከተማ ፖሊቲካ እንቅስቃሴና በገቢ አሰባሰብ ዙርያ ከከተማው ባለኃብቶች ጋር መክሯል፡፡

ማኅበራዊ ሚዲያን በመጠቀም የጥላቻና የግጭት መንስዔ የሚሆኑ አስተሳሰቦች በሃዋሳ ከተማ በስፋት እንደሚንፀባረቁና መንግሥት ህግ ተላልፈው በተገኙበት ላይ ሕጋዊ ዕርምጃ እንደሚወስድም ገልፀዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያዳምጡ።

የሃዋሳ ከተማ ዕጣ ፈንታ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:22 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG