በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በቡርኪና ፋሶ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሰዎች ተገደሉ


ቡርኪና ፋሶ ምስራቃዊ ክፍለ ግዛት ውስጥ ትናንት ማንነታቸው ያልታወቀ ታጣቂዎች አንድ ቤተ ክርስቲያን ላይ ተኩስ ከፍተው ቢያንስ አስራ አራት ሰው ገደሉ።

ጥቃቱ የደረሰው ከኒዠር ጋር በሚያዋስነው የቡርኪና ድንበር ላይ በምትገኝ ከተማ መሆኑ ተዘግቧ ዋል፤

የመንግሥቱ ወታደሮች አጥቂዎቹን ማደን ይዘዋል። ታጥቂዎቹ በቤተክርስቲያኑ ላይ ጥቃት የከፈቱት ምዕመናኑ የየሰንበት ቅዳሴ ስርዓት እየተከታተሉ በነበረበት ሲሆን አጥቂዎቹ በሞተር ብሽኪሊት ተሳፍረው እንዳመለጡ ነው የተዘገበው

ለጥቃቱ እስካሁን ኃላፊ ነኝ ብሎ የወጣ አካል የለም። ይሁን እንጂ ጽንፈኛ እስልምና አቀንቃኞች ናቸው ተብሎ ተጠርጥሯል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG