የፌዴራል መንግሥቱ፣ “ኦነግ ሸኔ” እያለ ከሚጠራው የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ጋራ፣ ሁለተኛ ዙር ድርድር እያካሔደ እንደኾነ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም፣ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የዩናይትድ ስቴትስ ዓለም አቀፍ የልማት ተራድኦ ድርጅት (USAID)፣ በመላው ኢትዮጵያ አቋርጦት የነበረውን የምግብ ድጋፍ እንዲቀጥል ስምምነት ላይ እንደተደረሰ ገልጿል፡፡
ዩኤስኤአይዲ፣ የምግብ ድጋፍ አቅርቦቱን እ.አ.አ. በመጪው ወር እንደሚቀጥል መግለጹ ይታወቃል፡፡
ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
መድረክ / ፎረም