በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ፈረንሣይ እናቶችና ህጻናትን ከሶሪያ አስመለሰች


ፎቶ ፋይል፦ ሶሪያ ሰሜናዊ ምስራቅ ሃሳካ ግዛት አል-ማሊኪያህ አቅራቢያ በሮጂ ካምፕ እአአ መጋቢት 28/2021
ፎቶ ፋይል፦ ሶሪያ ሰሜናዊ ምስራቅ ሃሳካ ግዛት አል-ማሊኪያህ አቅራቢያ በሮጂ ካምፕ እአአ መጋቢት 28/2021

ፈረንሣይ በሰሜን ሶሪያ ካምፖች የሚገኙ 35 ህጻናትና 16 እናቶቻቸውን ወደ ፈረንሳይ መመለሷን አስታወቀች፡፡

የፈረንሳይ የውጭ ጒዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ህጻናቱ ለማኅበራዊ ተንከባካቢ ድርጅቶች የተሰጡ ሲሆን የጤንነታቸው ሁኔታም ክትትል እንደሚደረግበት አስታውቋል፡፡

የእናቶቹ ጉዳይ ግን በፍርድ ቤት የሚይታይ መሆኑን ሚኒስቴሩ አመልክቷል፡፡

የሰአብዊ መብት ተሟጋች ቡድኖች በዩናይትድ ስቴትስ እየተመሩ እስላማዊ መንግሥት ቡድኖችን የሚዋጉ አገሮች እስላማዊ መንግሥትን ወታደራዊ ቡድን ለመቀላቀል የሄዱትንም ሆነ በግጭቱ ወቅት እዚያ የተወለዱ ዜጎቻቸውን እንዲያስመልሱ አሳስበዋል፡፡

XS
SM
MD
LG