በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አዲሱ የቡሩንዲ ፕረዚዳንት ቃለ - መሃላ ፈጸሙ


የቡሩንዲ አዲስ ፕረዚዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሽሜ
የቡሩንዲ አዲስ ፕረዚዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሽሜ

የቡሩንዲ አዲስ ፕረዚዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሽሜ በሀገሪቱ መዲና ጊቴጌ በሚገኘው ኢንጎማ ስቴድዮም፣ የፕረዚዳንትነት ቃለ - መሃላ ፈጸሙ። ፕረዚዳንት ፔር ንኩሩንዚዛ በድንገት ካረፉ፣ ሳምንት በሁዋላ ማለት ነው።

ንዳይሽሜ ቃለ - መሃላ እንዲፈጽሙ የታቀደው ባለፈው ነሃሴ ወር የነበረ ሲሆን በንኩሩንዚዛ ሞት ምክንያት ተራዝሟል። ይሁንና ተመራጩ ፕረዚዳንት በተቻለ ፍጥነት ቃለ-መሃላ እንዲፈጽሙ፣ የሀገሪቱ ህገ-መንግሥታዊ ፍርድ ቤት፣ ባለፈው ሳምንት ወስኗል።

አዲሱ የቡሩንዲ ፕረዚዳንት ባለፈው ግንቦት ወር በተካሄደው ምርጫ፣ 60 ከመቶ በላይ ድምጽ አግኝታው ማሸነፋቸው የሚታወስ ሲሆን ሥልጣን ላይ የሚቆዩትም ለሰባት ዓመታት ነው።

XS
SM
MD
LG