በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ሁለቱ ጋዜጠኞች ክስ ሳይመሰረትባቸው ከሦስት ወር በላይ መታሰራቸውን ቤተሰቦቻቸው ገለጹ


ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩና ጋዜጠኛ አናኒያ ሶሪ
ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩና ጋዜጠኛ አናኒያ ሶሪ

የአናኒያ ሶሪ ባለቤትና የኤልያስ ገብሩ እህት ጋዜጠኞቹ በጹሑፍ ሐሳባቸውን ከመግለጽ ውጭ የሠሩት ወንጀል የለም ብለዋል። መንግሥት በበኩሉ የታሰሩ ካሉ ወይ ሞያው የሚጠይቀውን የጋዜጠኝነት ሥነ ምግባር ባለማክበራቸው ነው ወይም ጋዜጠኞች ባለመሆናቸው ነው ብሏል።

አናንያ ሶሪና ኤልያስ ገብሩ የተባሉ ሁለት ጋዜጠኞችና የኢንተርኔት አምደኞች ክስ ሳይመሰረትባቸውና የታሰሩበትን ምክንያት በይፋ ሳይነገራቸው ከሦስት ወር በላይ በእስር ቤት እንደሚገኙ ቤተሰቦቻቸው ለአሜሪካ ድምጽ ገለጹ። ወጣቶቹ በጹሑፍ ሐሳባቸውን ከመግለጽ ውጭ የሠሩት ወንጀል የለም ብለዋል - ቤተሰቦቻቸው።

መንግሥት በበኩሉ የታሰሩ ካሉ ወይ ሞያው የሚጠይቀውን የጋዜጠኝነት ሥነ ምግባር ባለማክበራቸው ነው ወይም ጋዜጠኞች ባለመሆናቸው ነው ብሏል።

የጋዜጠኞች ደህንነት ተሟጋቹ ሲፒጄ ጋዜጠኞች እና ጦማሪያ የታሰሩት ስለፃፉ ብቻ ነው በአስቸኳይ ሊፈቱ ይገባል ማለቱ ይታወሳል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ።

ሁለቱ ጋዜጠኞች ክስ ሳይመሰረትባቸው ከሦስት ወር በላይ መታሰራቸውን ቤተሰቦቻቸው ገለጹ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:26 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG