አዲስ አበባ —
የኢትዮጵያ መንግሥት በዚምባቡዌ የሚደረግን የአመራር ለውጥ ከኮሎኔል መንግሥቱ ተላልፎ የመሰጠት ዕድል ጋር አያይዞ እንደማይመለከት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ግለሰቦችን የማደን ሳይሆን የፍርድ ቤትን ትዛዝ የማስፈፀም ግዴታና ኃላፊነት አለበት ብለዋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ መለስ አለም፡፡
በሌላም በኩል ግብፅ፣ መሪዋ ከኢትዮጵያና ከሱዳን አቻዎቻቸው ጋር ያፈረሙትን ስምምነት የሚጥስ ተግባር እየፈፀመች ነው ሲሉ ቃል አቀባዩ በትናንትናው ዕለት በሰጡት መግለጫ ገልፀዋል፡፡
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ