በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የባሕል ቤት ለኢትዮጵያ - በክሊቭላንድ


ከክሊቭላንዱ የኢትዮጵያ የባሕል መስክ
መሥራች አባላት ሁለቱ አቶ አክሊሉ ደምሴ እና Mr. Scott Embacher
ከክሊቭላንዱ የኢትዮጵያ የባሕል መስክ መሥራች አባላት ሁለቱ አቶ አክሊሉ ደምሴ እና Mr. Scott Embacher

ስለ ኢትዮጵያ ባሕል፣ ታሪክ እና ዘመን የጠገበ ሥልጣኔ የተሰየመ የባሕል መስክ ነው።

ከዓለም ዙሪያ ከተለያዩ አገሮች የመጡ ሕዝቦች የባሕል መናሀሪያ የሆነችው የክሊቭላንድ ከተማ ከማርቲን ሉተር ኪንግ ጎዳና እና ከአዋሳኙ የሮከፌለር መዝናኛ ፓርክ አቅራቢያ በተከለለው የልዩ ልዩ ውብ ባህላዊ ዕሴቶች መታሰቢያ ሥፍራ ዘንድሮ ለኢትዮጵያ የባሕል፣ ታሪክ እና ሥልጣኔ ቅርስ ሰላሳ ሶስተኛውን የባሕል መስክ ሰይማለች።

የኢትዮጵያ የባሕል ቤት በክሊቭላንድ
የኢትዮጵያ የባሕል ቤት በክሊቭላንድ

የዩናይትድ ስቴትሷ የኦሃዮ ክፍለ ግዛት ዋና ከተማ ክሊቭላንድ “ሰላም እርስ በእርስ በመግባባት” በሚል ተልዕኮ ከ103 ዓመታት በፊት እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር በ1916 ዓም የተጀመረ ለየቅል የሆኑ ባሕሎችን አብሮነትና መልከ ብዙነት የሚያወድስ የከበረ ልማድ ባለቤት ናት።

የኢትዮጵያ የባሕል ቤት በክሊቭላንድ
የኢትዮጵያ የባሕል ቤት በክሊቭላንድ

በቅርቡ የተመሠረተውን ይህን የኢትዮጵያ የባሕል መስክ በአስተባባሪነት ካቋቋሙ ስድስት ኢትዮጵያውንና አሜሪካውያን አጋሮቻቸው ሁለቱን አወያይተናል።

ከአቶ አክሊሉ ደምሴ ጋር የተካሄደውን ቃለ ምልልስ ከዚህ ያድምጡ።
please wait

No media source currently available

0:00 0:14:09 0:00
ከአቶ አክሊሉ ደምሴ ጋር የተካሄደውን ቃለ ምልልስ ከዚህ ያድምጡ።
please wait

No media source currently available

0:00 0:14:09 0:00

ከMr. Scott Embacher (በምርጫ ኢትዮጵያዊ ናቸው) ጋር የተካሄደውን ቃለ ምልልስ ከዚህ ያድምጡ።
please wait

No media source currently available

0:00 0:10:48 0:00
ከMr. Scott Embacher (በምርጫ ኢትዮጵያዊ ናቸው) ጋር የተካሄደውን ቃለ ምልልስ ከዚህ ያድምጡ።
please wait

No media source currently available

0:00 0:10:48 0:00


የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG