በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

"የኢትዮጵያ ሕፃናትና ባሕር ዘለል ጉዲፈቻ" ክፍል ሁለት


ባክነር/ብራይት ሆፕ ት/ቤት (ባንቱ/ኢትዮጵያ)
ባክነር/ብራይት ሆፕ ት/ቤት (ባንቱ/ኢትዮጵያ)

"ድኃይቱ ሃገር በበረከተ የውጭ ወረት እየነቀዘ ባለው ማኅበራዊ መዋቅር ላይ ዐይኗን ስታሣርፍ"

ኢትዮጵያ በአሥሮች የሚቆጠሩ ተቀባይነት ካለው ሥነ-ምግባር ተፃራሪ በሆነ ሁኔታ የሚንቀሣቀሱ ወላጆቻቸውን ያጡ ሕፃናት ማሣደጊያዎችን ለመዝጋት እያቀደች መሆኑን የአዲስ አበባው ሪፖርተራችን ፒተር ሃይንላይን ያስተላለፈው ዘገባ የመጀመሪያ ክፍል ቀደም ሲል መተላለፉ ይታወሣል፡፡

ያንን በማጭበርበርና በውንብድና አድራጎት ታጭቋል የተባለ፤ እንዲያውም ሥር ሰድዶ መንሠራፋቱና በገንዘብ ጥቅምም መተሣሰሩ የሚነገርለትን አሠራር ለማፅዳት ዓለምአቀፍ ድጋፍ ሊያስፈልግ እንደሚችል ፒተር በዘገባው ሁለተኛ ክፍል ጠቅሷል፡፡

"የአዲስ አበባውን ቦሌ ዓለምአቀፍ የአየር መናኸሪያ" ከመዋዕለ-ሕፃናት ጋር ለማምታታት የሚዳዳበት ጊዜ ጥቂት አይደለም" ብሎ ነው ፒተር የዘገባውን ሁለተኛ ክፍል የሚጀምረው፡፡ ግማሽ ለሚሆኑት መድረሻቸው ዩናይትድ ስቴትስ የሆነ በየቀኑ በአማካይ 12 ኢትዮጵያዊያን ሕፃናት በአዳዲሶቹ የውጭ አሣዳጊዎቻቸው እቅፍ ውስጥ እየሆኑ በዚህ በኩል ያልፋሉ፡፡

ከሰባት ዓመታት በፊት የባሕር ዘለሎቹ የጉዲፈቻ ልጆች ኢትዮጵያዊ የሚገኘው ከሁለት መቶ አንድ ነበር፡፡ ባለፈው ዓመት ግን ከአምስቱ አንዱ ኢትዮጵያዊ ሕፃን ነበር፡፡

ለዝርዝሩ ዘገባውን ያዳምጡ፡፡

XS
SM
MD
LG