በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ለሽብር ወንጀል ተከሣሾች የዋስትና ብይን የተቀጠረው ችሎት በዳኛ ቅያሬ ለሌላ ቀጠሮ ተላለፈ


ለሽብር ወንጀል ተከሣሾች የዋስትና ብይን የተቀጠረው ችሎት በዳኛ ቅያሬ ለሌላ ቀጠሮ ተላለፈ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:38 0:00

በሽብር ወንጀል በተከሠሡ ግለሰቦች የዋስትና ጉዳይ ላይ፣ ዛሬ ሊሰጥ የነበረው ብይን፣ በአንድ ዳኛ ቅያሪ ምክንያት ለሌላ ቀጠሮ ተላለፈ፡፡

በዳኛው መቀየር ምክንያት ውሳኔ አለመሰጠቱን የተቃወሙ ተከሣሾች፣ “በማንነታችን የታሰርን የፖለቲካ እስረኞች ነን፤ በፍትሕ ሥርዐቱ ላይም ጥርጣሬ አለን፤” ሲሉ አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ ዐቃቤ ሕግ በበኩሉ፣ “እስረኞቹ እንዲህ እያደረጉ ያሉት፣ በዳኞቹ ላይ ተጽእኖ ለማሳደር ነው፤ የሥነ ልቡና ጦርነት ነው፤” ሲል ተቃውሟል፡፡ የተከሣሽ ጠበቆችም፣ “እስረኞች ብሶታቸውንና ጥርጣሬያቸውን የመግለጽ መብት አላቸው፤” ብለው ተከራክረዋል፡፡

ችሎቱም በተመሳሳይ፣ ተከሣሾቹ ሐሳባቸውን የመግለጽ መብት እንዳላቸው ገልጾ፣ በዳኝነት ሒደቱ ላይ ግን ስጋት ሊኖር እንደማይገባ አስገንዝቧል፡፡አንድ ዳኛ ስለተቀየረበት ምክንያት፣ የከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንትን እንደጠየቁ የተናገሩት ከጠበቆች አንዱ ሰሎሞን ገዛኸኝ፣ “ጉዳዩ፣ የፍርድ ቤቱ አስተዳደራዊ ሥራ ነው፤” የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸው ተናግረዋል።

በተከሣሾች የዋስትና ጉዳይ ላይ ውሳኔ ለመስጠት ተቀጥሮ የነበረው የዛሬው ችሎት፣ ለቀጣዩ ሐምሌ 12 ቀን ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ችሎቱ ለዛሬ፣ ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም የተቀጠረው፣ በእነዶር. ወንድወሰን አሰፋ መዝገብ ሥር፣ ከአንድ ወር በፊት፣ በዐቃቤ ሕግ የሽብር ወንጀል ክሥ ከተመሠረተባቸው 51 ግለሰቦች መካከል፣ በእስር ላይ የሚገኙ ተከሣሾችን የዋስትና ጉዳይ በተመለከተ፣ ሰኔ 23 ቀን 2015 ዓ.ም. በነበረው ችሎት ክርክር ከተደረገ በኋላ ብይን ለመስጠት ነበር፡፡

ይኹንና፣ ጉዳዩን እየተመለከቱ ከሚገኙ ሦስት ዳኞች መካከል አንዱ(የግራ ዳኛው) ተቀይረው በሌላ ዳኛ እንደተተኩ የገለጸው ችሎቱ፣ ዛሬ፣ በዋስትናው ጉዳይ ላይ ብይን መስጠት እንደማይችልና በተለዋጭ ቀጠሮ እንደሚመለከተው አስታውቋል፡፡ በታሳሪዎች የተነሡ የመብት ጉዳዮችን ከአዳመጠ በኋላም፣ ከታሳሪዎች አስተያየት እና ጥያቄዎች ተሰንዝረዋል፡፡

XS
SM
MD
LG