በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በመግባቢያ ስምምነቱ ላይ ሐሰተኛ መረጃ እየተሰራጨ እንደሚገኝ ኢትዮጵያ ገለጸች


የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢዩ ተድላ
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢዩ ተድላ

ከራስ ገዟ ሶማሌላንድ ጋራ የተደረገውን የመግባቢያ ስምምት በተመለከተ፣ በማኅበራዊ የመገናኛ አማራጮች የሐሰት መረጃዎች እየተሰራጩ ናቸው፤ ሲል የኢትዮጵያ መንግሥት አስታውቋል፡፡

ኢትዮጵያ የመግባቢያ ስምምነቱን ለመሰረዝ እንደወሰነች”

“ኢትዮጵያ የመግባቢያ ስምምነቱን ለመሰረዝ እንደወሰነች” የሚገልጽ ይዘት ያለው መረጃ መሰራጨቱን ተከትሎ፣ ትላንት ረቡዕ፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መግለጫ ሰጥቷል፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢዩ ተድላ፣ የመግባቢያ ስምምነቱ የሚገኝበትን ደረጃ በተመለከተ “ወቅቱ ሲደርስ ይገለጻል” ሲሉ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡

በተያያዘ ቃል አቀባዩ፣ የኢትዮጵያ ወታደሮች ወደ ሶማሊያ ግዛት ጥሰው እንደገቡ፣ በሶማሊያ በኩል የቀረበውን ክስም “ሐሰት ነው” ሲሉ አጣጥለዋል፡፡

በመግባቢያ ስምምነቱ ላይ ሐሰተኛ መረጃ እየተሰራጨ እንደሚገኝ ኢትዮጵያ ገለጸች
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:39 0:00

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG