በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

"በዘመቻው ላይ የተነሱት ታሪኮች የኔም ልጅ ታሪክ ነው” - የሟች አርማዬ ዋቄ አባት


በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ "የኅሊና እስረኞችን ለማስታወስ" ለሚለው ዘመቻ የተጠቀሙበት ምስል።
በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ "የኅሊና እስረኞችን ለማስታወስ" ለሚለው ዘመቻ የተጠቀሙበት ምስል።

ዘመቻው ማረሚያ ቤቱ ውስጥ እየተፈፀመ ያለውን የመብት ጥሰት ምስል ያሳየ ነበር ያሉት አስተባባሪዎቹ ለአንድ ቀንም ቢሆን ብዙ ሰው የተሳተፈበትና የእስረኞቹ ታሪኮች የተነገሩበት ነው ብለዋል።

በአስተሳሰብና በአመለካከት ልዩነታቸው ብቻ በአሸባሪነት ተፈርጀው በእስር ላይ የሚገኙ እስረኞችን ለማሰብ በትናንትናው ዕለት በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የተደረገው የአንድ ቀን ዘመቻ የተሳካ እንደነበር አስተባባሪዎቹ ገልፀዋ።

“እስረኞችን ለማስታወስ በተካሄደው የኢንተርኔት ላይ ዘመቻ የተነሱት ታሪኮች የኔም ልጅ ታሪክ ነው” ያሉን ደግሞ በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በእስር ላይ የነበረ ልጃቸው እስር ቤት ውስጥ ተደብድቦ መሞቱን የገለጹ አባት ናቸው።

የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ አባዲ በእስር ቤቶችና በፖሊስ ጣቢያዎች ላይ የተደረገው የክትትል ሪፖርት በቅርቡ ይፋ እንደሚሆን ተናግረዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።

"በዘመቻው ላይ የተነሱት ታሪኮች የኔም ልጅ ታሪክ ነው” - የሟች አርማዬ ዋቄ አባት
please wait

No media source currently available

0:00 0:08:08 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG