አዲስ አበባ —
ከኢትዮጵያው ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ ጋር ያካሄዱት ውይይት መልካም እርምጃ መሆኑን ተሳታፊ የፖለቲካ ፓርቲዎች አስታወቁ። የተሻለ ውጤት እንዲገኝ ግን እንዲህ አይነቱ ውይይት ቀጣይነት ሊኖረው በቂ የመገናኛ ብዙሃን ሽፋንም ሊያገኝ እንደሚገባ አሳስበዋል። ከመነጋገር ሌላ መንገድ ሊኖር አይችልም ሲሉም ለአሜሪካ ድምጽ ሬድዮ አስረድተዋል።
ዘጋብያችን እስክንድር ፊረው በውይይቱ የተሳተፉ ሁለት ፓርቲዎች መሪዎችን አነጋገሮ ከአዲስ አበባ የላከው ዘገባ ዝርዝሩን ይዟል።