በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

“ወጥቼ ስመለስ የዐሥራ ሦስት ዓመት ልጄ አስክሬን ቤት ጠበቀኝ” የአወዳይ ከተማ ነዋሪ ወ/ሮ ኢፍቱ አብደላ


በዴሳ ከተማ
በዴሳ ከተማ

በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ ዞኖችና ወረዳዎች ላለፉት ዘጠኝ ወራት ሲካሄድ የነበረው ተቃውሞ ባለፉት ሁለት ሳምንታት በድጋሚ ማገርሸቱንና የሰባትና የ13 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ሕፃናትን ጨምሮ በርካቶች እየተገደሉ መሆኑን የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስና ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምፅ ተናገሩ። “ወጥቼ ስመለስ የዐሥራ ሦስት ዓመት ልጄ አስክሬን እቤት ጠበቀኝ” ያሉ የአወዳይ ከተማ ነዋሪም ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።

ተቃውሞው በምስራቅ እና ምዕራብ ሐረርጌ፣ በምዕራብ አርሲና በምዕራብ ሸዋም እንዳለ ነዋሪዎቹ ይናገራሉ። በምስራቅ ሐረርጌ አወዳይ ከተማ ነዋሪ እንደሆኑ የገለጹት አቶ መሐመድ አብዱራህማን “የዐስራ ሦስት ዓመት ልጄ ተገሎብኛል፤ ቀብሩ ላይ መገኘትም አልቻልኩም” ይላሉ።

በምስራቅ ሐረርጌ የሰላምና መረጋጋት ኃላፊ ኢንስፔክተር ግርማ ገላን በበኩላቸው ሞቱ ስለተባሉት ሰዎች የተጣራ መረጃ እንደሌላቸው ገልጸው ሰልፉን በተመለከተ የመንግስትን ንብረት ለማውደም የተነሱ የሽብር መልዕክተኞች ነበሩ ሁኔታውን ተቆጣጥረነዋል ብለዋል።

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።

“ወጥቼ ስመለስ የዐሥራ ሦስት ዓምት ልጄ አስክሬን ቤት ጠበቀኝ” የአወዳይ ከተማ ነዋሪ ወ/ሮ ኢፍቱ አብደላ
please wait

No media source currently available

0:00 0:08:02 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ


XS
SM
MD
LG