በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሚፈቱም የሚታሠሩም ዛሬም መኖራቸውን ኦፌኮ ገለፀ


ከአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጋር ተያይዞ ለተቃውሞ የወጡ የኦሮሚያ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎች
ከአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጋር ተያይዞ ለተቃውሞ የወጡ የኦሮሚያ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎች

የኦሮሞ ተማሪዎች ጥያቄ ከጀርባው “የቀለም አብዮት” አራማጆች እጅ አለበት ሲሉ አንድ የመንግሥት ባለሥልጣን ተናግረዋል፡፡





አቶ ሬድዋን ሁሴን - የመንግሥት ኮምዩኒኬሽንስ ጉዳዮች ፅ/ቤት ኃላፊ
አቶ ሬድዋን ሁሴን - የመንግሥት ኮምዩኒኬሽንስ ጉዳዮች ፅ/ቤት ኃላፊ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:47 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

ባለፉት ሣምንታት በኦሮሚያ የተለያዩ ክፍሎች ተቀስቅሶ በነበረው የተማሪዎች ተቃውሞና የተከተለው ሁከት ምክንያት “ከታሠሩት አንዳንዶቹ የተፈቱ ቢሆንም ዛሬም እሥሩ ቀጥሏል” ሲሉ የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ ዋና ፀሐፊና የመድረክ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ገልፀዋል፡፡
አቶ በቀለ ነጋ - የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ዋና ፀሐፊ
አቶ በቀለ ነጋ - የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ዋና ፀሐፊ
አቶ በቀለ ዛሬ ለቪኦኤ በሰጡት መግለጫ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ለነገ በስተያ ቅዳሜ የጠራው ሰልፍም ዓላማው የኢትዮጵያ ሕዝብ የመንግሥትን የግድያና የእሥራት እርምጃ በአንድነት የሚቃወምበት መድረክ መፍጠር መሆኑን ተናግረዋል።

በሌላ በኩል ደግሞ የመንግሥት ኮምዩኒኬሽንስ ባለስልጣናት የኦሮሞ ተማሪዎች ተቃውሞ ሕጋዊ መሆኑን ጠቅሰው ከእንቅስቃሴው በስተጀርባ ግን “የቀለም አብዮት” ያሉትን የሚያራምዱ ሊኖሩ እንደሚችሉ ለአገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ገልፀዋል።

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የመለስካቸው አምሃን ዘገበ ያዳምጡ።
XS
SM
MD
LG