በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የዕሁዱን የሕዝበ ሙስሊም ስብሰባ መንግሥት ሕገወጥ ነው አለ


ሰደቃው ሰላማዊና ኃይማኖታዊ ነው በመሆኑ የሚቋረጥበት ምክንያት የለም ሲሉ አንድ የሕዝበ ሙስሊሙ ጥያቄዎች መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባል አስታወቁ፡፡

(ይህ ገፅ ሲከፈት የተደራረቡ ወይም የተረበሹ ድምፆችን የሚሰሙ ከሆነ ኮምፕዩተርዎ ከአንድ በላይ ድምፅ ማጫወቻ አለው ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ከዚህ ፅሁፍ ሥር ካሉት ማጫወቻዎች አንደኛውን ብቻ አስቀርተው ሌሎቹን ያቁሟቸው፡፡)

ሐይማይኖትን ሽፋን ያደረጉ አንዳንድ ወገኖች የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ስብሰባ በሚካሄድበት ቀን የተከለከለና ሕገወጥ ስብሰባ ለማድረግ እየተዘጋጁ ነው ሲል ፌደራል ፖሊስ አስጠንቅቋል፡፡

በሌላ በኩል ግን በአዲስ አበባ መስጊዶች የፀሎት ሥነ-ሥርዓት ወይም ሰደቃ ለማድረግ ዕሁድ ሐምሌ ስምንት ቀን የተያዘው የሙስሊም አማኒያን ፕሮግራም ሠላማዊ ነው፤ የሐይማኖት ጉዳይ ነው፤ በታሰበው መሠረት ይካሄዳል ሲሉ የሕዝበ ሙስሊሙ ጥያቄዎች መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ ከሚል ሸምሱ ለቪኦኤ አመልክተዋል፡፡

የመንግሥትን ማስጠንቀቂያ የሚመለከተውን ዘገባና ከአቶ ከሚል ሸምሱ ጋር የተደረገውን ሙሉ ቃለምልልስ ከተያያዘው ፋይል ያዳምጡ፡፡

(ገፁ ሲከፈት የተደራረቡ ወይም የተረበሹ ድምፆችን የሚሰሙ ከሆነ ከማጫወቻዎቹ አንደኛውን ብቻ አስቀርተው ሌሎቹን ያቁሟቸውየሚጫወተውን እንደገና ያስጀምሩት፡፡ )


XS
SM
MD
LG