ዋሽንግተን ዲሲ —
ያለፈው ሳምንት በአዲስ አበባ ከተማ “ቆሼ” እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ለሚኖሩ ነዋሪዎች አስከፊ ነበር። ምክኒያቱ ያልታወቀ የቆሻሻ መደረመስ አደጋ የበርካታ ሰዎችን ሕይወት ቀጥፏል። መንግስት በአደጋው 113 ሰው ሕይወት መጥፋቱን አስታውቋ። በዛሬው ዕለት በአካባቢው የነበሩ እማኞች ዛሬ ቦታው እየተቆፈረ እንደሆነ ገልፀዋል።
ለመሆኑ የአስክሬን ቁፋሮው ፍለጋው ምን ይመስል ነበር?
በሕይወት የተረፉትና የተፈናቀሉት ሰዎች እርዳታ እየደረሳቸው ነው ወይ? በቀጣይስ የሚዋጣው ገንዘብ እንዴት ይደርሳቸዋል?
ጽዮን ግርማ እነዚህንና ሌሎች ጥያቄዎችን አንስታ በቀጣይ ባጠናቀረችው ዘገባ ትዳስሰዋለች።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ