በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በጋምቤላ የታጣቂዎች ጥቃት ተሠነዘረ


የተገደሉና የቆሰሉ አሉ

በጋምቤላ ክልል ታጣቂዎች ትናንት ማምሻውን በፈፀሙት ጥቃት አራት ኢትዮጵያዊያንና አንድ የፓኪስታን ዜጋ መገደላቸው ተገለፀ፡፡

የክልሉን ፖሊስ የጠቀሱት የመንግሥት መገናኛ ብዙኃን እንዳሉት አራት ኢትዮጵያዊያንና አራት ፓኪስታናዊያን ደግሞ ከባድና ቀላል የመቁሰል አደጋ ደርሶባቸዋል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ ተገደሉ የተባሉት ፓኪስታናዊያን ቁጥር አንድ ሣይሆን አራት መሆናቸውንና በአጠቃላይ የሞቱት ሰዎች ቁጥር አሥራአንድ መድረሱን ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ የተባለ ድርጅት ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡

ዝርዝሩን ያድምጡ፡፡

ተመሳሳይ ርእስ

XS
SM
MD
LG