በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የታገዱ ሃያ አይሮፕላኖች እንዲበሩ ተፈቀደ


የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን
የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን

የኢትዮጵያን የአየር ክልል በመጣሳቸው በቁጥጥር ሥር ውለው የነበሩት ሃያ አይሮፕላኖችና አብራሪዎቻቸው በመንግሥት ውሣኔ ጉዟቸውን እንዲቀጥሉ መደረጉን የሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን አስታውቋል፡፡

አብራሪዎቹ ጋምቤላ የደረሱት ክልከላ በይፋ ከተነገራቸው በኋላ መሆኑን የባለሥልጣኑ ዳይሬክተር ጄነራል ኮሎኔል ወሰንየለህ ሁነኛው ለአሜሪካ ድምፅ ገልፀዋል፡፡

በአዲስ አበባ የሚገኘው የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲም አብራሪዎቹ ጉዟቸውን መቀጠላቸውን አረጋግጧል፡፡

የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን ዳይሬክተር ጄነራል የሆኑትን ኮለኔል ወሰንየለህ ሁነኛውን ያነጋገርው እስክንድር ፍሬው ተካታዩን ልኳል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ።

የታገዱ ሃያ አይሮፕላኖች እንዲበሩ ተፈቀደ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:05 0:00

XS
SM
MD
LG