አዲስ አበባ —
በኳታርና በሌሎች የሰላጤው ሀገራት መካከል የተፈጠረው ውዝግብ በሰላማዊ መንገድ መፈታቱን አንደምትደግፍ ኢትዮጵያ አስታወቀች፡፡
ዛሬ ከኳታሩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሱሉጣን ቢል ሳዓድ አል ማኡርኪ ጋር የተወያዩት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ላይ ገለልተኛ አቋም እንዳላት አስረድተዋል፡፡
የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቀደም ሲል ባወጣው መግለጫም በኩዌት የተጀመረውን የሰላም ጥረት እንደሚደግፍ ጠቁሟል፡፡
የባህረ ሰላጤው ሀገራት በኳታር ላይ የጣሉት ማዕቀብ ይሔንንም ተከትሎ የተፈጠረው ውዝግብ አሁንም መቋጫ አላገኘም፡፡
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ