በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በኢትዮጵያና ኤርትራ ድንበር ውጊያ እንደነበር የሁለቱም ሀገሮች መንግስታት አስታወቁ


የኢትዮጵያና ኤርትራ ድንበር
የኢትዮጵያና ኤርትራ ድንበር

የኤርትራ ማስታወቂያ ሚንስቴር ባወጣው መግለጫ፤ የኢትዮጵያ መንግሥት ሰኔ 5 ቀን ጥቃት ሰንዝሯል ብሏል። የኢትዮጵያ መንግስት ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ በበኩላቸው የኤርትራ መንግስት ለማጥቃት ያደረገውን ሙከራ ቀልብሰናል ብለዋል።

በተያያዘ ዜና፥ በሰሜን ኢትዮጵያ፥ በትግራይ ምሥራቃዊ ክልል በተለይ በገርሁ ስርናይ እና ዛላአምበሳ የገጠር አካባቢዎች ነዋሪዎች ትላንት ከንጋቱ 10 ጀምሮ የተኩስ ልውውጥ መስማታቸውን በድምበር ከተሞች የሚኖሩ የዐይን ምስክሮች ለአሜሪካ ድምፅ ሬድዩ ገለፁ።

ግርማይ ገብሩ በስልክ ያነጋገራቸው በድምበሩ አካባቢ የሚኖሩ ሰዎች እንደሚገልፁት ሕብረተሰቡ በተለይም ዛሬ ተረጋግቶ ዕለታዊ ኑሮውን በማካሄድ ላይ ይገኛል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ድምጽ ያድምጡ።

በኢትዮጵያና ኤርትራ ድንበር ውጊያ እንደነበር የሁለቱም ሀገሮች መንግስታት አስታወቁ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:38 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

XS
SM
MD
LG