ዋሺንግተን ዲሲ —
የኢትዮጵያው አስቸኳይ ጊዜ ዓዋጅ፣ ባለፈው ዓመት በኦሮሚያ ክልል ተጀምሮ በተለይም በሰሜኑ የአማራው ክልል ከነበረው ሕዝባዊ አለመረጋጋት ጋር በተያያዘ ለብዙ ሺሕ ሰዎች ወህኒ መውረድ ምክንያት ሆኗል። ከታሳሪዎቹ መካከል ጋዜጠኞችና ጦማርያን ይገኙባቸዋል።
ማርቲ ቫንዳር ወልፍ ከዛሬው የዓለም የፕሬስ ነፃነት ቀን ቀደም ብላ፣ ከሦስቱ የኢትዮጵያ ብሎገሮች ጋር ያደረገችውን ውይይት፣ ለቪኦኤ ልካለች፡፡
በዘገባውም የዩኒቨርሲቲ መምህርና ሃያሲ ሥዩም ተሾመ፣ ለጀርመኑ ራድዮ ጣቢያ ዶቼ ቬሌ በሰጡት ቃለ መጠይቅ ላይ የመንግሥቱን እንከን በመናገራቸው፣ በጥቅምት ወር ለሁለት ወራት እስር ቤት ቆይተዋል።
ከተፈቱ በኋላም፣ በሳምንት በተደጋጋሚ ጊዜያት በተለያዩ የፖለቲካ ዓምዶችና ማኅበራዊ ድረ ገፆች ላይ ፁሑፎችን አውጥተዋል።
ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ