አዲስ አበባ —
በሙስና የተጠረጠሩ ሠላሳ አራት የመንግሥት ባለሥልጣናትና የሥራ ኃላፊዎች እንደዚሁም ባለሃብቶችና በመሃል አሉ የተባሉ ደላሎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የኢትዮጵያ መንግሥት አስታወቀ።
እርምጃው በተሃድሶ እንቅስቃሴው ወቅት የተገባው ቀል ተግባራዊ የተደረገበት መሆኑን የመንግሥት ኮምዩኒኬሽንስ ጉዳዮች ፅሕፈት ቤት ኃላፊ ሚኒስትር ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ ለአሜሪካ ድምፅ አመልክተዋል።
ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ሥር የማዋሉ ሂደት እንደቀጠለ መሆኑንም ኃላፊው ገልፀዋል።
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ