በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኢትዮጵያ አየር መንገዱ ሰማኒያ ዓለምቀፍ በረራዎችን አቋረጠ


የኢትዮጵያ አየር መንገዱ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ስጋት ወደ 80 ዓለምቀፍ በረራዎቹን ማቋረጡን ባወጣው መግለጫ አስታወቀ።

በዓለምቀፍ ደረጃ የሚደረጉ የካርጎ /የዕቃ ማመላለሻ/ በረራዎች እንደቀጠሉ ጠቁሞ፣ ዕርምጃው የተወሰደው የኮሮናቫይረስን ለመከላከልና ለመቆጣጠር መሆኑንም አስታውቋል።

የሀገር ውስጥ በረራ ተጓዦች ቁጥር በ50 በመቶ መቀነሱን፣ ወደ ሁሉም የሀገር ውስጥ መዳረሻዎቹ የሚሰጠውን አገልግሎት አለማቋረጡን ጭምሮ ገልጿል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG