ከ2 አመት በፊት የተቋቋመው የባቱ ባልቻ አባነፍሶ ት/ቤት አቅም የሌላቸውን ወላጆች ለመርዳት ታስቦ ነው፡፡ ተመስገን ደምሰው በዚህ ት/ቤት ለመማር እድሉን ካገኙት ህጻናት አንዱ ነው፡፡ ወደፊትም ሐኪም መሆንን ይመኛል፡፡
ለማስተማር እና ለማሳደግ አቅም ከሌላቸው ቤተሰቦች ውስጥ አንዷ ሮዛ መሀመድ ሲሆኑ ይህንን ዕድል ልጃቸው ባታገኝ ኖሮ እጣ ፋንታዋ ከባድ ይሆን እንደነበር ጠቅሳለች፡፡
የአሜሪካ ከፍተኛ የልኳን ቡድን ጉብኝቱ አላማም፤ ታዳጊዎች ከቤተሰባቸው ጋር ሆነው ድጋፍ የሚያገኙበትን ሁኔታ መመልከት ነበር፡፡