በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ፈርስት ሂጅራ ፋውንዴሽን የመንፈቀ ረመዳን ኢፍጣር መርሐ ግብር አካሔደ


ፈርስት ሂጅራ ፋውንዴሽን የመንፈቀ ረመዳን ኢፍጣር መርሐ ግብር አካሔደ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:49 0:00

ፈርስት ሂጅራ ፋውንዴሽን የመንፈቀ ረመዳን ኢፍጣር መርሐ ግብር አካሔደ

ሙስሊሞችን ለማገዝና በዓላትን በኅብረት ለማክበር ዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው በሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ የተመሠረተው ፈርስት ሂጅራ ፋውንዴሽን፣ ባለፈው ቅዳሜ፣ መጋቢት 14 ቀን 2016 ዓ.ም. የረመዳን ጾም አጋማሽ የኢፍጣር መርሐ ግብር አድርጓል።

ዝግጅቱ ለዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ለሚገኙ የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ማኅበረሰብ ምስጋና ለማቅረብም መዘጋጀቱን ፋውንዴሽኑ ገልጿል፡፡ ይህም፣ ባለፉት ጥቂት ወራት ከማኅበረሰቡ በተሰበሰበው የ1ነጥብ8 ሚሊዮን ዶላር መዋጮ፣ ለመስጂድ እና ለትምህርት ቤት አገልግሎት የሚውል ሰፊ መሬት ለመግዛት ከመቻሉ ጋራ የተያያዘ እንደኾነ፣ የፈርስት ሂጅራ ፋውንዴሽን የቦርድ ፕሬዚዳንት ጀማል ያሲን አስረድተዋል።

ኤደን ገረመው፣ ከ39 ዓመታት በፊት በተመሠረተው ፋውንዴሽን ባካሔደው የኢፍጣር መርሐ ግብር ላይ ተገኝታ ያሰናዳችው ዘገባ በመቀጠል ይቀርባል።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG