ከዋሺንግተን ዲሲ እና ከአቅራቢያው ግዛቶች የተሰባሰቡ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ዓመታዊውን የ"ምስጋና እና አንድነት ኢፍጣር" በቨርጂኒያ አካሒደዋል።
የእስልምና እምነት ተከታዮች በአንድ ስፍራ ተገናኝተው ማዕድ በተጋሩበት ምሽት፣ ለማኅበረሰቡ ለሚበጁ ግንባታዎች የሚውል ድጋፍም ተሰባስቦበታል። የረመዳን ጾምን ድባብ የሚያጎሉ መልዕክቶች ተላልፈውበታል ፣ ኃይማኖታዊ ሥርዓቶችም ተከናውነውበታል።
በአናንዴል ቨርጂኒያ የተከናወነውን ሥነ ስርዐት የተከታተለው ሀብታሙ ስዩም በአጭሩ ያስቃኘናል።
መድረክ / ፎረም