በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኢትዮጵያና ሩሲያ በራሳቸው ገንዘብ ሊገበያዩ ነው


ፎቶ ፋይል፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከብሪክስ በመሪዎች ጉባኤ ላይ ሩሲያ እአአ ጥቅምት 23/2024
ፎቶ ፋይል፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከብሪክስ በመሪዎች ጉባኤ ላይ ሩሲያ እአአ ጥቅምት 23/2024

ሩሲያ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሦስት የአፍሪካ ሀገራት ጋራ በሀገር ውስጥ ገንዘብ ለመገበያየት የሚያስችላትን መመርያ ይፋ አድርጋለች፡፡

የሀገሪቱ የገንዘብ ሚንስቴር ይፋ በአደረገው መመርያ ሀገራቱ ከሩሲያ ጋራ በሚፈጽሙት ግብይት የሚያጋጥማቸውን የውጭ ምንዛሪ እጥረት ለመቅረፍ እና የተሻለ የንግድ ግንኙነት ለመፍጠር እንደሚያግዝ አስታውቋል፡፡ ከዚህ በፊት ከተባበሩት አረብ ኢምሬቶች ጋራ ተመሳሳይ ስምምነት መፈጸሙን ያስታወቀው የኢትዮጵያ መንግሥት በዚህ ጉዳይ ላይ ግን እስካሁን ያለው ነገር የለም፡፡

ፕሬዝደንት ትረምፕ በትሩዝና ሶሻል በተሰኘው የማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ኢትዮጵያ አባል የሆነችበት ብሪክስ የተሰኘው ማኅበር አባል ሃገራት የጋራ መገበያያ ለመፍጠር የሚያደርጉትን ጥረት እንዲያቆሙ በተደጋጋሚ ሲያስጠነቅቁ መቆየታቸው ይታወሳል።

ኢትዮጵያና ሩሲያ በራሳቸው ገንዘብ ሊገበያዩ ነው
please wait

No media source currently available

0:00 0:09:45 0:00

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG