በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በተመድ የኤርትራ አምባሳደር ግርማ አስመሮም አረፉ


አምባሳደር ግርማ አስመሮም
አምባሳደር ግርማ አስመሮም

በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኤርትራ ቋሚ ተጠሪ ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩት አምባሳደር ግርማ አስመሮም አረፉ፡፡

በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኤርትራ ቋሚ ተጠሪ ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩት አምባሳደር ግርማ አስመሮም አረፉ፡፡

አምባሣደሩ ትናንት ኒው ዮርክ ላይ በስድሣ ስድስት ዓመት ዕድሜአቸው ማረፋቸው የታወቀው ዛሬ ሲሆን ላለፉት ዘጠኝ ወራት በሕመምና በሕክምና ላይ እንደነበሩ ታውቋል፡፡

አምባሣደር ግርማ ወደ ኒው ዮርክ ከመላካቸው በፊት በኢትዮጵያና በአፍሪካ ኅብረት፣ እንዲሁም በዩናይትድ ስቴትስና በካናዳ የኤርትራ አምባሣደር ሆነው አገልግለዋል፡፡

አምባሣደር ግርማ ዋሺንግተን ዲ.ሲ. ከሚገኘው አሜሪካን ዩኒቨርሲቲ በዓለምአቀፍ ግንኙነቶች በማስተርስ ዲግሪ ተመርቀዋል፡፡

አምባሣደር ግርማ አስመሮም በወጣትነት ዕድሜአቸው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሄራዊ ቡድን ተጫዋችና በአምስት ቁጥር ቦታ ተከላካይ፤ እንዲሁም በሰባት ቁጥር ቦታ የሚሰለፉ አጥቂ ነበሩ፡፡

አምባሣደር ግርማ ባለትዳር ነበሩ፡፡

XS
SM
MD
LG