አዲስ አበባ —
ኢትዮጵያ የአባይን ውኃ ለልማት ስትጠቀም የግብፅንም ሆነ የሱዳን ፍላጎት እንደምትረዳና ድርሻቸውንም እንደምታከብር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ አስታውቀዋል።
ዶ/ር አብይ አሕመድ ወደ ጠቅላይ ሚኒስትርነቱ ሥልጣን ከመጡ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ግብፅ ተጉዘው በዚያ የሥራ ጉብኝት አድርገዋል።
በአባይ ወንዝ ላይ የሚገነባውን ኅዳሴ ግድብ አስመልክቶ ከግብፅ ጋር ያለው ልዩነት ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ዋነኛ ፈተናዎች አንዱ እንደሚሆን ሲነገር ቆይቷል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ዛሬ አዲስ አበባ የደረሱትን ከግብፅ እሥር ቤቶች ያስለቀቋቸውን ሰላሣ ሁለት ኢትዮጵያዊያን ይዘው የገቡት እራሳቸው በበረሩበት አይሮፕላን አሳፍረው ነው።
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ