በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኢቦላ ህክምና በኮንጎ


ዲሞክራሲያዊት ኮንጎ ሪፐብሊክ ውስጥ የኢቦላ ህሙማንን ለማከም ጥቅም ላይ እየዋሉ ካሉት አራት በሙከራ ላይ ያሉ መድሃኒቶች ውስጥ፣ ሁለቱ ፍቱንነታቸው በሚገባ መረጋገጡ ተገለፀ። በዚህም ምክንያት በበሽታው ለተያዙ ሁሉ ሊሰጡ መሆኑ ተመልክቱዋል ።

/Regn-eb3 and Mab -114/ የተባሉት መድሃኒቶች ያስገኙት ውጤታማነት ሳይንቲስቶቹ መድሃኒቶቹ ላይ የያዙትን ጥናት አቋርጠው ለአንድ ዓመት በዘለቀው ወረርሺኝ ከ1800 በላይ ሰዎች በሞቱባት በኮንጎ ጥቅም ላይ እንዲውል ማድረግ ላይ እንዲያተኩሩ አድርጓል።

የኮንጎ የሥነ ህይወትና ህክምና (ባዮሜዲካል) ምርምር ብሄራዊ ተቋም ዳይሬክተር ዣን ዣክ ሙዬምቤ “ከእንግዲህ ኢቦላ ተይዞ አለመዳን አከተመ፤ አሁን የተገኘው ስኬት ብዙ ሺዎችን ህይወት ያተርፋል” ብለዋል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG