በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በሺርካ ወረዳ ሃይማኖት የለየ በተባለ ጥቃት 36 ምእመናን ሲገደሉ ቀሪዎቹ እንደሸሹ ተገለጸ


በሺርካ ወረዳ ሃይማኖት የለየ በተባለ ጥቃት 36 ምእመናን ሲገደሉ ቀሪዎቹ እንደሸሹ ተገለጸ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:01 0:00

በሺርካ ወረዳ ሃይማኖት የለየ በተባለ ጥቃት 36 ምእመናን ሲገደሉ ቀሪዎቹ እንደሸሹ ተገለጸ

በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሺርካ ወረዳ፣ ባለፈው አንድ ሳምንት ውስጥ፣ ታጣቂዎች ፈፀሙት በተባለ ማንነት ተኮር ጥቃት፣ 36 ምእመናን እንደተገደሉ፣ አንድ የስፍራው ነዋሪ፣ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡

ለደኅንነታቸው በመስጋት ስማቸውን እንዳንጠቅስ የጠየቁን ነዋሪው፣ ከሟቾቹ መካከል ዐሥር የአንድ ቤተሰብ አባላት እና ስምንት የሌላ ቤተሰብ አባላት እንደሚገኙበት ገልጸዋል፡፡

ሟቾቹ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች እንደኾኑና ጥቃቱም በሃይማኖታዊ ማንነት ላይ ያተኮረ እንደኾነ፣ ነዋሪው አክለው አመልክተዋል፡፡

የክልሉ የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን ቢሮ ሓላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ፣ ጥቃቱን የፈጸመው፣ መንግሥት “ኦነግ ሸኔ” ብሎ የሚጠራው ዐማፂ ኃይል ነው፤ ብለዋል፡፡

በመንግሥት “ኦነግ ሸኔ” የተባለው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ቃል አቀባይ ኦዳ ታርቢ ውንጀላውን አስተባብለዋል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG