በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

“ተምች” መሰል “ትል” የምሥራቅ አፍሪካ ሀገሮች እየተዛመተ ነው


ፎቶ ፋይል
ፎቶ ፋይል

ከአንድ ዓመት በላይ በምዕራብ እና ደቡባዊ አፍሪካ አዝመራ ላይ ከባድ ጥፋት ሲያደርስ የከረመው “ተምች መሰል ትል” ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ታንዛኒያ፣ ዩጋንዳ እና ሩዋንዳን ጨምሮ ወደ አብዛኞቹ የምሥራቅ አፍሪካ ሀገሮች እየተዛመተ መሆኑ ተገለፀ።

ከአንድ ዓመት በላይ በምዕራብ እና ደቡባዊ አፍሪካ አዝመራ ላይ ከባድ ጥፋት ሲያደርስ የከረመው “ተምች መሰል ትል” ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ታንዛኒያ፣ ዩጋንዳ እና ሩዋንዳን ጨምሮ ወደ አብዛኞቹ የምሥራቅ አፍሪካ ሀገሮች እየተዛመተ መሆኑ ተገለፀ።

የምዕራብ ኬንያ ነዋሪ የሆኑ ቲመቲ ሚባያ

“ባለፈው ሚያዝያ ወር ተምቹ፣ ሰባ አምሥት ከመቶው በቆሎዬን አውድሞብኛል” ብሉዋል።

የአፍሪካ አረንጓዴ አብዮት ሕብረት /Alliance for a Green Revolution in Africa/ የተባለው ድርጅት የፕሮግራም ምክትል ፕሬዚዳንት ጆ ዴቭሬስ በሰጡት ማብራሪያ በእንግሊዝኛ “ Fall Armyworm” ተብሎ የሚጠራው የአዝርዕት ተባይ መጀመሪያ ላይ የተከሰተው እአአ 2016 ዓ.ም. ጥር ወር ውስጥ ናይጄሪያ ውስጥ ሲሆን በፍጥነት እየተዛመተ በዚህ ባሳለፍነው መጋቢት ኬንያ ደርሷል ብለዋል።

የአዝርዕቱ ተባይ ለመጀመሪያ ጊዜ የገባው በዚህ ዓመት ሲሆን ከዚህ ቀደም አይተውትም ሆነ እንዴት መቆጣጠር እንደሚቻል ስለማያውቁ፣ ሰብላቸውን አውድሞባቸዋል - ገበሬዎቹንም አሳስቧል ብለዋል።

አሜሪካ ሃገሮች ውስጥ የተለመዱት እነዚህ በራሪ ተባዮች ረጅም ርቀት መብረር የሚችሉና ሴቷ ባንዴ አንድ ሺህ ዕንቁላል መጣል እንደምትችል ሳይንቲስቶች ይናገራሉ።

በዚህ ምክንያት ቆላማ አየር ንብረት ባላቸው አካባቢዎች ስለሚዛመቱ መሆኑን የሚናገሩት ባለሙያዎች መጀመሪያ እንዴት ወደ አካባቢው ሊደርሱ እንደቻሉ ግን እስካሁን ግልፅ አይደለም ብለዋል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG