በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በፓኪስታን የአፍጋኒስታንን የሰላም ሂደት የሚያነጋግር የአራትዮሽ ድርድር እየተካሄደ ነው


የአፍጋኒስታን ደፒውቲ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሀክማት ከሊል ካርዛይ (Hekmat Khalil Karzai) (ቅኝ) እና የፓኪስታን የውጭ ጉዳይ ሚኒስተር አማካሪ ሳርታጅ አዚዝ (Sartaj Aziz) ከየአራት አገሮች ስብሰባ በፊት ሰላም እየተባባሉ (ፎቶ አሶሽየተድ ፕረስ/AP)
የአፍጋኒስታን ደፒውቲ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሀክማት ከሊል ካርዛይ (Hekmat Khalil Karzai) (ቅኝ) እና የፓኪስታን የውጭ ጉዳይ ሚኒስተር አማካሪ ሳርታጅ አዚዝ (Sartaj Aziz) ከየአራት አገሮች ስብሰባ በፊት ሰላም እየተባባሉ (ፎቶ አሶሽየተድ ፕረስ/AP)

ፓኪስታን የአፍጋኒስታንን የሰላም ሂደት ለማንሰራራት ስለሚቻልበት መንገድ የሚነጋገር የአራትዮሽ ድርድር በማስተናገድ ላይ ነች።

አፍጋኒስታን፣ ቻይና እና ዩናይትድ ስቴትስ የሚካፈሉበት ድርደር በፓኪስታን እየተካሄደ ነው። ፓኪስታን የአፍጋኒስታንን የሰላም ሂደት ለማንሰራራት ስለሚቻልበት መንገድ የሚነጋገር የአራትዮሽ ድርድር በማስተናገድ ላይ ነች ።

የፓኪስታን ጠቅላይ ምኒስትር ናዋዝ ሻሪፍ የውጭ ጉዳይ አማካሪ ሳርታዥ ኣዚዝ ውይይቱን በንግግር ከፍተዋል።

የዕርቀ ሰላሙ ሂደት ዋና ዓላማ ታሊባኖቹን ወደድርድሩ ጠረጴዛ እንዲመጡ ማድረግና የፖለቲካ ግባቸውን ለማሳካት ሁከትን እንዳይጠቀሙ ማበረታቻ መስጠት ነው ብለዋል።

የአፍጋኒስታን ጸጥታ ሃይሎች ከታሊባን ዓመጽ ተዋጊውችት ጋር በ ባልክ (Balkh)ክልል ኩንዱዝ (Kunduz) ከተማ ሰሜን ካቡል (Kabul)ውስጥ እየተዋጉ እአአ 2015
የአፍጋኒስታን ጸጥታ ሃይሎች ከታሊባን ዓመጽ ተዋጊውችት ጋር በ ባልክ (Balkh)ክልል ኩንዱዝ (Kunduz) ከተማ ሰሜን ካቡል (Kabul)ውስጥ እየተዋጉ እአአ 2015

አፍርጋኒስታን ውስጥ ባለፈው አንድ ዓመት የታሊባን ዓመጽ እየተስፋፋ መምጣቱ ጦርነት በበጣጠቃት ሃገር የባሰ ደም መፋሰስና አለመረጋጋት ይመጣል የሚል ስጋት ፈጥሯል። የዜና ዘገባችንን ለማዳመጥ ከዚህ በታች ያለውን የድምጽ ፋይል ይጫኑ።

የአፍጋኒስታንን የሰላም ሂደት የሚያነጋግር የአራትዮሽ ድርድር በፓኪስታን
please wait

No media source currently available

0:00 0:00:54 0:00

XS
SM
MD
LG