በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የዲሲ ከንቲባ አዲስ አበባ ይገባሉ


ኢ/ር ታከለ ኡማ እና የዋሽንግተን ዲሲ ከንቲባ ምዩሪየል ባውዘር
ኢ/ር ታከለ ኡማ እና የዋሽንግተን ዲሲ ከንቲባ ምዩሪየል ባውዘር

ዋሽንግተን ዲሲ ከንቲባ ምዩሪየል ባውዘር ከፊታችን ቅዳሜ ጀምሮ ይፋዊ ጉብኝት ለማድረግ አዲስ አበባ እንደሚገቡ በዩናይትድ ስቴትስ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል።

ከከንቲባዋ ጋር ከሃምሣ በላይ አሜሪካዊያን የንግድ ማህበረሰብ አባላት እንደሚጓዙ ተገልጿል።

ዋሺንግተን የመገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ለልዑካን ቡድኑ ገለፃ ማድረጉን አስታውቋል።

እህትማማች ከተሞች የሆኑት አዲስ አበባና ዋሽንግተን ስምምነታቸውን በአዲስ መልክ ያድሳሉ ተብሏል።

ከንቲባዋ ወደ አዲስ አበባ የሚጓዙት የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ አቶ ታከለ ኡማ ዋሽንግተን ዲሲ በነበሩ ጊዜ ባደረጉላቸው ግብዣ መሠረት መሆኑን ኤምባሲው አክሎ ጠቁሟል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG