እያነጋገሩ ባሉ ወቅታዊ የኢትዮጵያ ጉዳዮች ዙሪያ የተጀመረ ተከታታይ ክርክር ነው።
የዕለተ-አርብ እሰጥ አገባ ተከራካሪዎች፤ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች እየታዩ ላሉት ሕዝባዊ ተቃውሞች መንስኤዎችና እንዲሁም በተደጋጋሚ ለሚነሱት የሕዝብ ጥያቄዎች ሁነኛ ምላሽ በየፊናቸው ይቃኛሉ።
ዘለቄታ ባላቸው የፖለቲካ ጥያቄዎችም የመፍትሔ አማራጮች የሚሏቸውን እንደየ-አመለካከታቸው ዝንባሌ በክርክራቸው ይወረውራሉ።
የክርክር ፕሮግራሙ ተሳታፊዎች የገዢውን ፓርቲ አቋምና ፖሊሲዎች በመደገፍ የቀረቡት አቶ ኤልያስ ግደይ ከአዲስ አበባ፤ የተቃውሞ ድምጽ የሚያሰሙት ደግሞ አቶ ግዛው ለገሰ ናቸው፤ ከዋሽንግተን ዲሲ።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ