ዋሺንግተን ዲሲ —
እአአ በ2014 ሶቼ ባዘጋጀችው የክረምት ኦሎምፒክ ውድድር ወቅት አበረታች መድሃኒት በመውሰድ የተከሰሱ 28 የሩሲያ አትሌቶች፣ ያስመዘገቧቸው ውጤቶች እንዲሠረዙና ዕድሜ ልክ ከኦሎምፒክ ውድድሮች እንዲተገዱ መደረጋቸው ይታወሳል። ጉዳዩን ሲያይ የቆየው ዓለምቀፉ የስፖርት ይግባኝ ፍ/ቤት ዛሬ ብይኑን ሠርዞ የአትሌቶቹን አቤቱታ አፅድቋል።
በሌላ በኩል ደግሞ ደቡብ ኮሪያ በምታዘጋጀው ኦሊምፒክ የምትሳተፈው የኮሚኒስት ሰሜን ኮሪያ ሰንደቅ ዓላማ ዛሬ በአትሌቶቿ መንደር ውስጥ መውለብለብ ጀምሯል።
ክሪስ ሃናስ እና ሪቻርድ ግሪን ከቪኦኤ ዜና ማደራጃ ያጠናቀሯቸው አጫጭር ዘገባዎች አሉ።
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ