በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ቦዪንግ አመነ፤ ይቅርታ ጠየቀ


737 ማክስ ጄቶቹ ላይ የቴክኒክና የንድፍ ችግር እንደነበረባቸው አምራቹ ቦይንግ ኩባንያ ለመጀመሪያ ጊዜ በአደባባይ አምኗል።

የኩባያው ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዴኒስ ምዩለንበርግ በዩናይትድ ስቴትስ የተወካዮች ምክር ቤት ፊት ቀርበው ትናንትና ትናንት ሲጠየቁ ስሕተትና ጥፋት መፈፀሙን አምነው “እኔም ልቤ ተሰብሯል፤ በጥልቅ አዝናለሁ” ብለዋል።

የኩባንያቸው መታመን እንደገና እንዲያንሠራራ ለማድረግ በርትተው እንደሚሠሩና እንዲያ ዓይነት ጥፋት እንደማይደገምም ለሕግ መወሰኛ ምክር ቤቱ የንግድ፣ የሣይንስና የትራንስፖርት ኮሚቴ ተናግረዋል።

የተጎጂዎች ቤተሰቦችና የሕግ ተወካዮቻቸውም ተገኝተዋል።

የቦዪንግ ከፍተኛ ኃላፊዎችና የሚመለከታቸው የመንግሥት ባለሥልጣናት ዛሬም በተወካዮች ምክር ቤቱ የትራንስፖርት ኮሚቴ ፊት ቀርበው ተጠይቀዋል።

የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

ቦዪንግ አመነ፤ ይቅርታ ጠየቀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:21 0:00


የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG