በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በሺሕ የሚቆጠሩ ሰዎች ከኮንጎ ወደ ቡሩንዲ ሸሹ


የኤም 23 አማፅያን ከደቡብ ኪቩ ግዛት አስተዳደር ቢሮ ውጭ በኮንጎ ሁለተኛ ትልቅ ከተማ ቡካቩ መሃል እአአ የካቲት 16/2025
የኤም 23 አማፅያን ከደቡብ ኪቩ ግዛት አስተዳደር ቢሮ ውጭ በኮንጎ ሁለተኛ ትልቅ ከተማ ቡካቩ መሃል እአአ የካቲት 16/2025

በሩዋንዳ የሚደገፉት የኤም 23 አማጺያን ጥቃት እያየለ ባለበት በዚህ ወቅት፣ አሥር ሺሕ የሚሆኑ የኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ዜጎች ባለፉት ሦስት ቀናት ድንበሯን አቋርጠው መግባታቸውን ቡሩንዲ አስታውቃለች፡፡

ወታደርቶችን ከሲቪሎች ለመለየትና በተመድ የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን አማካይነት መጠለያ ለመስጠት ጥረት በመደረግ ላይ መኾኑን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር በመግለጫው አስታውቋል።

በሩዋንዳ የሚደገፉት የኤም 23 አማጺያን ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ በምሥራቅ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ሰፊ ሥፍራዎችን የተቆጣጠሩ ሲኾን፣ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ በደቡብ ኪቩ ግዛት ቡካቩ የተሰኘችውን ቁልፍ ከተማ ተቆጣጥረዋል። ሥፍራው ከቡሩንዲ ድንበር 50 ኪ. ሜ. ርቀት ላይ የሚገኝ መሆኑም ታውቋል።

በሺሕ የሚቆጠሩት የኮንጎ ዜጎች ወደ ቡሩንዲ የሸሹት የቡካቩ መያዝ አስደንግጧቸው እንደሆነ ታውቋል።

ቡሩንዲ ባለፈው ዓርብ ፍልሰቱን ለመግታት ስትል ለተወሰኑ ሰዓታት ድንበሯን ዘግታ እንደነበር ባለሥልጣናት አስታውቀዋል።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG