ዋሺንግተን ዲሲ —
የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ፣ የቀድሞውን የኤፍቢአይ ዳይሬክተር ጄምስ ኮሜን ወቀሱ። ምክንያት፣ አዲስ ለፃፉት መፅሐፍ ትርፍ ማግኛ ሲሉ የቀድሞውን የደኅንነት ኃላፊ የማይክል ፍሌን ሕይወት አበላሸተዋል በማለት።
ትረምፕ በትዊተር ባስተላለፉት መልዕክት ኮሜ በፍሌን ደረሰባችው ያሉትን በደል ዘርዝረው አውጥተዋል።
ኮሜ የፃፉት ማስታወሻ ለዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት የተላከ ሲሆን፣ የፍትኅ ሚኒስቴር ነው በትናንቱ ዕለት ወደ ኮንግረስ የሰደደው። በኋም ለተለያዩ መገናኛ አውታሮች ደርሶ ለሕዝብ መቅረቡ ታውቋል።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ