በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የምዕራባውያን ማዕቀብ እያየለ በመጣበት ብሪክስ የላቀ ሚና እንዲኖረው ስትል ቻይና አሳሰበች


የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ፣ የሩስያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ እና የብራዚል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማውሮ ቪዬራ በሩስያ ኒዝሂ ኖቭጎሮድ ከተማ ብሪክስ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ላይ እአአ ሰኔ 11/2024
የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ፣ የሩስያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ እና የብራዚል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማውሮ ቪዬራ በሩስያ ኒዝሂ ኖቭጎሮድ ከተማ ብሪክስ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ላይ እአአ ሰኔ 11/2024

በሃገራቸው የተጣሉ የምዕራባውያን ማዕቀቦች እና የንግድ ገደቦች እያየሉ በመጡበት ብሪክስ ራሱን ሁሉን አቀፍ አካል አድርጎ እንዲመሰርት እና አባል ሃገራት ከፍ ያሉ ኃላፊነቶችን እንዲወስዱ ቻይና ታሳስባለች ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዋንግ ዪ ዛሬ ማክሰኞ ተናገሩ።

በርካታ የቻይና ኩባንያዎች ሩስያ በዩክሬን የምታካሂደውን ጦርነት በመደገፋቸው ለምዕራባውያን ማዕቀብ ገጥሟቸዋል። ከዚህ በጨማሪ የአውሮፓ ኮምሽን በኢሌክትሪክ ኃይል የሚንቀሳቀሱ እና ረከስ ባለ ዋጋ የሚሸጡት አነስተኛ ቻይና ሰር አውቶሞቢሎች በአውሮፓ መኪና አምራቾች ላይ የሚያስድሩትን ተጽዕኖ ለመከላከል በያዝነው ሳምንት አዲስ የቀረጥ ድንጋጌ ይፋ ያደርጋል ተብሎ ተጠብቋል።

የሰባቱ የዓለም ባለ ጸጋ አገራት ቡድን በያዝነው ሳምንት ‘ሩስያን ከምዕራባውያኑ ዓለም ማዕቀብ ተጽዕኖ እንድታመልጥ ለማድረግ እየረዱ ናቸው’ ያላቸውን አነስተኛ መጠን ያላቸውን የቻይና ባንኮች የተባሉትን ድርጊታቸውን እንዲያቆሙ የታለመ ጠንካራ ማስጠንቀቂያ ያስተላልፋሉ’ ተብሎ እንደሚጠበቅ ሮይተርስ ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል።

ብራዚልን፣ ሩስያን፣ ህንድን፣ ቻይናን፣ እና ደቡብ አፍሪቃን፤ እንዲሁም ኢራንን፣ ግብጽን፣ ኢትዮጵያን እና የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስን ጨምሮ ዘጠኝ አባል አገራት ያሉት የምጣኔ ሃብት ሕብረት የሚንስትሮች ጉባኤ በሩስያዋ የኒዝኒ ኖቭጎሮድ በመካሄድ ላይ ነው።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG