በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በጭላሎ ተራራ ደን እሳት ቃጠሎ የተያዘው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ


የጭላሎ ተራራ ደን በእሳት እንዲቃጠል ያደረገው ግለሰብ በ7 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ የተፈረደበት መሆኑን የሃገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ዘገቡ።

የጭላሎን ፓርክ ደን ለጊዜው ካልተያዙ ሁለት ግለሰቦች ጋር ጥር 23 ቀን 2011 ዓ.ም 11 ሰዓት ላይ በእሳት እንዲያያዝ ማድረጋቸውን አቃቤ ህግ በክሱ ጠቅሷል።

ሁለቱ ተጠርጣሪዎች ለጊዜው ሲሰወሩ ተከሳሹ በአካባቢው ነዋሪዎች እጅ ከፍንጅ መያዙ ተገልጿል። ተከሳሹና ግብረ አበሮቹ በለኮሱት እሳት ከ800 ሄክታር በላይ ደን መውደሙን በመግለፅ አቃቤ ህግ በጢዮ ወረዳ ፍርድ ቤት ክስ መመስረቱም ተገልጿል።

ለሦስት ቀናት የዘለቀውን የእሳት ቃጠሎ የአካባቢው ነዋሪዎች ለማጥፋት ተረባርበዋል። እሳቱን ለማጥፋት የሰው ኃይልን ጨምሮ ከ210 ሺ ብር በላይ ወጪ ሆኗል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG