በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ካሜሩን ከስልሳ በላይ ት/ቤቶች ተዘጉ

ካሜሩን ከናይጀሪያ ጋር በሚዋስነው ሰሜናዊ ድንበርዋ ላይ፣ ተማሪዎችንና አስተማሪዎችን እየጨመረ ከሄደው የቦኮ ሃራም ጥቃት ለማዳን ስትል፣ ከስልሳ በላይ የሚሆኑ ትምህርት ቤቶችን፣ እንደገና እንደዘጋች አስታውቃለች።

የማዕከላዊ አፍሪካይቱ ሃገር፣ ከመኖርያቸው የተፈናቃሉት ተማሪዋች፣ የተሻለ ደኅንነት አለው በሚባል አካባቢ እንዲማሩ፣ ወታደሮች መመደብዋ ታውቋል።

ቦኮ ሃራም የሃገሪቱ ወታደራዊ ኃይል በሚወስደው እርምጃ በመዳከሙ፣ በአጥፍቶ መጥፋት ዘዴ ላይ ማትኮሩ ተዘግቧል።

This item is part of
XS
SM
MD
LG