ለጥያቄዎቻችሁ መልስ የሚሰጡት በአንድ ዓመት በላይ ለሆነ ጊዜ ታስረው የቆዩትና በቅርቡ የተፈቱት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ - ኦፌኮ ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና ናቸው፡፡
ዶ/ር መረራ ድርጅታቸው በኢትዮጵያ አንድነት ፅኑ እምነት እንዳለው በማስረዳት የትግል ዓላማው በተከታታይ መንግሥት ሲጨቆን ለኖረው የኦሮሞ ሕዝብ ሰብዓዊ ዲሞክራሲያዊ መብቱን ለመመለስ ነው ይላሉ፡፡
የኦሮምኛ ቋንቋ ከአማረኛ በተጨማሪ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ፌደራላዊ ቋንቋ እንዲሆን የሚደግፉት፣ የሀገሪቱን አንድነት ለማጠናከርና በትምህርት ቤቶቹ በንግድና በማንኛውም መስክ በሕዝብ መሃል መግባባት እንዲሰፍን ነው፡፡
የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ