በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በሰደድ እሳት የተጎዳችው ካሊፎርኒያ አሁን ደግሞ ጎርፍ አስግቷታል


ፎቶ ፋይል - በአልታዴና በእሳት የወደሙ የመኖሪያ ቤቶች፤ ካሊፎርኒያ፣ እአአ ጥር 21/2025
ፎቶ ፋይል - በአልታዴና በእሳት የወደሙ የመኖሪያ ቤቶች፤ ካሊፎርኒያ፣ እአአ ጥር 21/2025

በሰደድ እሳት የተጎዳው ካሊፎርኒያ ግዛት ከፍተኛ ዝናብ እና ንፋስን ተከትሎ ሊከሰት ይችላል ለተባለው ጎርፍ በመዘጋጀት ላይ ነች፡፡ የአካባቢው ባለሥልጣናት እና የነፍስ አድን ዋናተኞች ጎርፉን ለመከላከል ነዋሪዎች አሸዋ የተሞሉ ጆንያዎች እንዲወስዱ አሳስበዋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የኦሬገኗ ፖርትላንድ ከተማ አውራ ጎዳናዎቿን ብዛት ያለው የግግር በረዶ መከላከያ አልብሳለች፡፡ በተጨማሪም የኦሪገን እና አይዳሆ ግዛት ባለሥልጣናት ከዛሬ ሐሙስ ጀምሮ ለሚመጣ የበረዶ እና የበረዶ ውሽንፍር ለመዘጋጀት የአደጋ ጊዜ መጠለያዎችን አዘጋጅተዋል። የብሔራዊ የአየር ሁኔታ አገልግሎት ደቡባዊ ካሊፎርኒያ በተራሮች ላይ እስከ ስድስት ኢንች ዝናብ፤ እንዲሁም በባህር ዳርቻ አካባቢዎች እና ሸለቆዎች ደግሞ ዝናብ በብዛት ሊጥል እንደሚችል ተንብየዋል፡፡ ዝናቡ ኃይለኛ ዛፎችን ሊጥል እና የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ሊያስከትል የሚችል እንደሚኾን ስጋት አለ።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG