በአሜሪካ ሎስ አንጀለስ ከተማ እና በአካባቢው የተቀሰቀሰውን የሰደድ እሳት መስፋፋት ለመግታትና ለማጥፋት እየተደረገ ካለው መጠነ ሰፊ ርብርብ በአንጻሩ፣ እስከ አሁን ለመቆጣጠር አልተቻለም።
እንዲያውም ከፍተኛ ፍጥነት ባለው ነፋስ ደረቅ በመታገዝ እየተባባሰ ያለው የሰደድ እሳቱ፣ በየሰዓቱ የሚያደርሰው ውድመት አስከፊ እንደኾነ ነው የተገለጸው። የጠፋውም እሳት ቢኾን፣ ረመጡ በደረቁ ነፋስ ዳግም ሊቀሰቀስ እንደሚችል መጠቆሙ ተጨማሪ ስጋት አጭሯል።
የአሜሪካ ድምጿ ቬሮኒካ ባልደራስ ኢግሌሲያስ ያደረሰችንን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
መድረክ / ፎረም