በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በቡርኪና ፋሶ ከአንድ ዓመት ባነሰ ጊዜ ከ250 በላይ ሰዎች መገደላቸው ተገለፀ


ፎቶ ፋይል
ፎቶ ፋይል

ቡርኪና ፋሶ ላይ ከአንድ ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ከ250 በላይ የሚሆኑ ሰዎች እስላማዊ መንግሥት ነኝ በሚለው ጽንፈኛ ቡድን መገደላቸውን ሂዮመን ራይትስ ዋች የተባለው የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ዛሬ ባወጣው ዘገባ ገልጿል።

በምዕራብ አፍሪካቱ ሀገር ሰሜንና ምስራቅ ክፍል ጥቃቶች እየተበራከቱ መሆናቸውና ታጣቂዎች የሚቆጣጠርዋቸው ግዛቶች እየጨመሩ መሄዳቸዋን ሂዮመን ራይትስ ዋች አክሏል።

አጥቂዎቹ የሚገድልዋቸው ሰዎች ከመንግሥትና ከምዕራባውያን ጋር ግንኙነት አላቸው። ወይም ክርስትያኖች ናቸው በሚል መሆኑን እማኞች መናገራቸውን የሰብአዊው መብት ተሟጋቹ ቡድን ጠቅሷል።

አማፅያኑ አርሶ አደሮችን፣ አማንያንን፣ የማዕድን ሰራተኞችንና ነጋዴዎችን ሆን ብለው ዒላማ እንደሚያደርጉ የሂዮማን ራይትስ ዋች የምዕራብ አፍሪካ ጉዳይ ሥራ አስኪያጅ ኮሪን ዱፍካ ገልፀው፣ የጦርነት ወንጀል ነው ብለውታል።

አንሱር ዐል-ኢስላምን የመሳሰሉት ከዐል-ቓዒዳ ጋር ወይም እስላማዊ መንግስት ነኝ ከሚለው ቡድን ጋር የተሳሰሩ አማጽያን ካለፈው ዓመት ሚያዝያ ወር አንስተው ቢያንስ 20 ጥቃቶች አካሄደዋል። በጥቃቶቹም ቢያስንስ 256 ስዎች ተገድለዋል ይላል የሂዮማን ራይትስ ዋች ዘገባ።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG