በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የብሪታንያ ምክር ቤት


 brexit
brexit

የአውሮፓው ህብረት ዋና ተደራዳሪ ማይክል ባርኒየር ብሪታንያ ከህብረቱ የምትወጣበት ሥምምነት ሳይደረግ ፍቹ ሊፈፀም ወደ ሚችልበት ሁኔታ እየተጠጋች ነው ብለዋል።

ባርኔየር ብራሰልስ ሆነው ባደረጉት ንግግር አሁንም ቢሆን ብሪታንያ ካለ ምንም ሥምምነት መውጣቱን ለማስወገድ የምትችልበት ተስፋ አለ ብለዋል። ይሁንና ብሪታንያ ያሏት አማራጮች ውሱን መሆናቸውን ገልፀዋል። የብሪታንያ ምክር ቤት ቴሬሳ ሜይ ከአውሮፓ ህብረት ጋር ለሁለት ዓመታት ያህል ከተነጋገሩ በኋላ የተደረሰውን ሥምምነት ቢቀበል እንደሚያዋጣው ነው ዋናው ተደራዳሪ የመከሩት።

እስካሁን ባለው ጊዜ የብሪታንያ ምክር ቤት ሥምምነቱን ሦስት ጊዜ አልተቀበለውም። ቴሬሳ ሜይ ለአርተኛ ጊዜ ድምፅ እንዲሰጥበት ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG